በፊሊፒንስ የአሜሪካዊያን አፈና እና ግድያ

ወሮታ ለፍትሕ ስለ አቡ ሳይፍ ግሩፕ (ኤኤስጂ) መሪ ኻዳፋ ጃንጃላኒ መረጃ ለሰጡ ግለሰቦች በድምሩ $5 ሚሊዮን ወሮታ ክፍሏል፡፡ በግንቦት 30 ቀን 1999 ዓ.ም. በፊሊፒንስ የአሜሪካ አምባሳደር በዚህ በጆሎ ደሴት በተካሄደው ይፋዊ የወሮታ አከፋፈል ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተዋል፡፡
ኻዳፋይ ጃንጃላኒ በፊሊፒንስ የሚንቀሳቀሰው ሽብርተኛ ድርጅት ከኤኤስጂ ከፍተኛ አመራር አባላት መካከል አንዱ ነበር፡፡ ጃንጃላኒ ለፊሊፒንስ እና የአሜሪካ ዜጎች መታፈን እና ሞት በኃላፊነት ይጠየቃል፡፡ ጃንጃላኒ ለማርቲን እና ጋርሲያ በርንሃም እና ከሁለት ሌሎች የአሜሪካ ዜጎች መታፈን ጋር ግንኙነት አለው፤ እንዲሁም ለዩናይትድ ስቴትስ ዜጋ ጉዊሌርሞ ሶቤሮ መቀላት በቀጥታ ተጠያቂ ነው፡፡ በተጨማሪም ጃንጃላኒ የዩናይትድ ስቴትስን ጥቅሞች ዒላማ ያደርጉ ጥቃቶች ለምሳሌ በማኒላ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ላይ የቦምብ ጥቃት ለመፈጸም ሲካሄድ የነበረ ሴራ፣ በየካቲት 1996 ዓ.ም. የሱፐርፌሪ 14 መስጠም እና የ1997 ዓ.ም. የቫለንታይን ቀን ሦስት የቦምብ ጥቃቶችን ያቀደ እና ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን፣ በእነዚህም በድምሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሞተዋል ወይም ቆስለዋል፡፡
በጥር 08 ቀን 1999 ዓ.ም. የፊሊፒንስ የጦር ኃይል በመረጃ ሰጪዎች ባገኘው መረጃ ላይ በመመስረት ጃንጃላኒን ለመያዝ ኦፕሬሽን አካሄደ፤ በዚህም እንቅስቃሴ ወቅት ጃንጃላኒ በከባዱ ቢቆስልም እንኳን ለማምለጥ ቻለ፡፡ በቀጣዮቹ ወራት ደግሞ ጃንጃላኒ ሞቷል የሚል ወሬ መናፈስ ጀመረ፡፡ በጥር 1999 ዓ.ም. ሁለት ግለሰቦች ስለ ጃንጃላኒ አስከሬን መገኛ መረጃ ይዘው መጡ፡፡ የዲኤንኤ ምርመራ ካካሄደ በኋላ ኤፍቢአይ ጃንጃላኒ በእውነትም መሞቱን አረጋግጧል፡፡ በእነዚህ ሰዎች የተሰጡ መረጃዎች ሁሉ የጃንጃላኒን መገኛ እና ማንነቱንም ለመለየት ወሳኝ ሆነው ተገኝተዋል፡፡
መረጃ ይስጡ
እርስዎ የበኩልዎን ያድርጉ፡፡ ደህንነቱ የተጠበቀ ዓለም እና ይበልጥ ብሩህ የወደፊት ጊዜን እውን ያድርጉ፡፡ ስለ ወሮታ ለፍትሕ መረጃ ማቀበያ ወይም ቅረቢያ አማራጮች ለማወቅ በዚህ ክሊክ ያድርጉ፡፡
- ታጋቺዎች/ተጠላፊዎች
- ሰሜን ኮሪያ
- ጣልቃገብነት በምርጫ ውስጥ
