Success stories
በኮሎምቢያ የአሜሪካዊያን አፈና .

ወሮታ ለፍትሕ የሪቮሉሽነሪ አርምድ ፎርስስ ኦፍ ኮሎምቢያ (ኤፍኤአርሲ) ኮማንደር ስለ ኤድጋር ናቫሮ መረጃ ለሰጡ ሦስት ሰዎች በድምሩ የ$900,000 ወሮታ ከፍሏል፡፡
በየካቲት 1995 ዓ.ም. ቶማስ ሆዌስ፣ ኬኔት ስታንሴል እና ማርክ ቮንሳልቬስ የዮናይትድ ስቴትስ አውሮፕላናቸው በኮሎምቢያ ጫካ ውስጥ በተከሰከሰበት ጊዜ ታፍነው ተወሰዱ፡፡ ይህ ቡድን እና የዚህ ድርጊት ተመሳጣሪዎች ሁለት ሌሎች በአውሮፕላኑ ተሳፍረው የነበሩ ሁለት ሰዎች፡- ቶማስ ጃኒስ የተባለ የአሜሪካ ዜጋ እና ሉዊስ አልሴዲስ ክሩዝ የተባለ የኮሎምቢያ ዜጋ ገድለዋል፡፡
የሪቮሉሽነሪ አርምድ ፎርስስ ኦፍ ኮሎምቢያ (ኤፍኤአርሲ) ቲዮፊሎ ፎሬሮ ሞባይል ኮለም ምክትል አዛዥ ናቫሮ በዚህ አፈና ውስጥ ተሳትፎ ነበረው ተብሎ ይጠረጠራል፡፡
በጥቅምት 06 ቀን 1996 ዓ.ም. ወሮታ ይከፈለናል በሚል ሃሳብ ሦስት መረጃ ሰጪዎች ለኮሎምቢያ ወታደሮችን ወደ ናቫሮ እና የሌሎች የቡድኑ አባላት መገኛ መርተዋል፡፡ ናቫሮ ከወታደሮች ጋር በነበረ የተኩስ ልውውጥ ተገድሏል፡፡ በቀጣይ በተካሄደ የኮሎምቢያ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ሦስቱ አሜሪካዊያን በሰኔ 25 ቀን 2000 ዓ.ም. ሊተርፉ ችለዋል፡፡
መረጃ ይስጡ
እርስዎ የበኩልዎን ያድርጉ፡፡ ደህንነቱ የተጠበቀ ዓለም እና ይበልጥ ብሩህ የወደፊት ጊዜን እውን ያድርጉ፡፡ ስለ ወሮታ ለፍትሕ መረጃ ማቀበያ ወይም ቅረቢያ አማራጮች ለማወቅ በዚህ ክሊክ ያድርጉ፡፡
- ታጋቺዎች/ተጠላፊዎች
- ሰሜን ኮሪያ
- ጣልቃገብነት በምርጫ ውስጥ
