ስለ ተቋሙ
ወሮታ ለፍትሕ ስለ ዊሊያም በክሌ እገታ እና ግድያ መረጃ ለሚሰጥ እስከ $5 ሚሊዮን ወሮታ ይከፍላል፡፡ በክሌ በሊባኖስ የሲአይኤ ጣቢያ ኃላፊ ነበር፤ በ1975 ዓ.ም. በቤይሩት የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ላይ የቦንብ ጥቃት ከተፈጸመ በኋላ ይህንን ኃላፊነት በበጎ ፈቃደኝነት በ1975 ዓ.ም. ተረከበ፡፡ በመጋቢት 07 ቀን 1976 ዓ.ም. በርክሌይ ወደ ሥራ በመሄድ ላይ እያለ ታገተ፡፡ በግንቦት 26 ቀን 1977 ዓ.ም. በእስር ላይ እያለ ከመሞቱ በፊት ምርመራ እና ስቃይ ተፈጽሞበታል፡፡ በርክሌይ ለአስር ዓመታት ያህል በቆየው የሊባኖስ የእገታ ቀውስ በአብዛኛው የምዕራባዊያን አገራት ዜጎች ከነበሩ፣ በሂዝባላህ እና ከሂዝባላህ ጋር ግንኙነት በነበራቸው ሽብርተኞች ከታገቱ 100 ተጎጂዎች መካከል አንዱ ነበር፡፡
