ስለ ተቋሙ
ወሮታ ለፍትሕ በ1995 በካራቺ፣ ፓኪስታን በ2 የዩናይትድ ስቴትስ ቆንስላ ጀነራል ሰራተኞች ላይ ስለተፈፀመ ግድያ መረጃ ለሚሰጥ እስከ $5 ሚሊዮን ወሮታ ይከፍላል፡፡ በየካቲት 29 ቀን 1987 ዓ.ም. አንድ ነጭ ቫን ተሽከርካሪ የዩናይትድ ስቴትስ ቆንስላ ሰራተኞችን አሳፍሮ በመጓዝ ላይ ሳለ በተጨናነቀ አካባቢ አንድ ቢጫ ታክሲ ፊት ለፊቱ በድንገት በመግባት እንዲቆም አስገደደው፡፡ ሌላ መኪና ደግሞ ቫኑ እንዳይንቀሳቀስ አገደው፡፡ ፊታቸውን በጭንብል የሸፈኑ ሽብርተኞች አውቶማቲክ ጠመንጃ በመያዝ በቫኑ ላይ ተኩስ ከፍተው ሁለት የቆንስላውን ሰራተኞች ሲገድሉ በአንዱ ላይ ጉዳት አድርሰዋል፡፡
