ስለ ተቋሙ
ወሮታ ለፍትሕ በ1991 ዓ.ም. በብዊንዲ ፓርክ፣ ዩጋንዳ በቱሪስቶች ላይ ስለተፈፀመው ጥቃት መረጃ ለሚሰጥ እስከ $5 ሚሊዮን ወሮታ ይከፍላል፡፡
በየካቲት 22 ቀን 1991 ዓ.ም. የሯንዳ ነፃነት ሰራዊት (ኤኤልአይአር) አባላት ያልታጠቁ ቱሪስቶች እና በእነርሱ ጋይዶች ላይ በብዊንዲ ለመግባት ጥብቅ ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ጥቃት ፈፅመዋል፡፡ ይህ የቱሪስት ቡድን ላይ ጥቃት ተፈፅሞ፣ ታግቶ ወደ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በእግሩ እንዲጓዝ ተደርጓል፡፡ አንድ ፖል ሮስ ዋጋባ የተባለ የኡጋንዳ ዜጋ በህይወት እና በእሳት ተቃጥሏል፡፡ ከስምንቱ የጥቃቱ ሰለባዎች መካከል ሱዛን ሚለር እና ሮበርት ሀውብነር የተባሉ አሜሪካውያን በድብደባ ተገድለዋል፡፡
በጥቃት ፈፃሚዎቹ መሪ ከጥቃቱ በህይወት ለተረፉ ተጎጂዎች በእጅ የተፃፈ ማስታወሻ ተሰጥቶ ነበር፡ በዚህ ማስታወሻ ጥቃቱ የተፈፀመው ዩናይትድ ስቴትስ እና ሌሎች አገራት ለሯንዳ መንግስት ድጋፍ መስጠታቸውን እንዲያቆሙ መልዕክት ለማስተላለፍ ነበር፡፡
