ስለ ተቋሙ
ወሮታ ለፍትሕ በየመን የሚንቀሳቀሰው የአረብ ባሕረሰላጤ አል-ቃዒዳ (ኤኪውኤፒ) ተብሎ የሚታወቀውን ሽብርተኛ ድርጅት የፋይናንስ ማግኛ ዘዴዎችን ለማሰናከል የሚያስችል መረጃ ለሚሰጥ እስከ $10 ሚሊዮን ወሮታ ይከፍላል፡፡
ሱባይት ቢን ሃሪት ከፍተኛ የአረብ ባሕረሰላጤ አል-ቃዒዳ መሪ እና የዚህ ቡድን የሹራ ምክር ቤት አባል ነው፡፡
ይህ ግለሰብ በሌላ ስሙ አቡ ጋዛዋን አል-ሃድራሚ ተብሎ ይጠራል፤ ግለሰቡ የቡድኑን የፋይናንስ እንቅስቃሴ ከመምራቱም ባሻገር የውጭ አገር ዜግነት ያላቸውን ተዋጊዎች ጉዞ አስተባብሯል፡፡
