Success stories
የአሜሪካዊያን ግድያ
ወሮታ ለፍትሕ በታኅሳስ 27 ቀን 1985 ዓ.ም. ሁለት በማዕከላዊ የመረጃ ኤጀንሲ (ሲአይኤ) ዋና መሥሪያ ቤት ወደሚገኘው ሥራቸው በመሄድ ላይ በነበሩ ሠራተኞች ላይ ተኩስ ከፍቶ ግድያ የፈጸመውን ሚር ኤይማል ካንሲ በቁጥጥር ሥር ለማዋል ያስቻለ መረጃ ለሰጠ ግለሰብ ወሮታ ከፍሏል፡፡

ካንሲ በማዕከላዊ የመረጃ ኤጀንሲ (ሲአይኤ) ዋና መሥሪያ ቤት ፊት ለፊት በሚገኝ የትራፊክ መብራት ቆመው በነበሩ ተሽከርካሪዎች ላይ ያለ ማስጠንቀቂያ ወይም አንዳችም ትንኮሳ ሳይደረግበት ተኩስ ከፈተ፡፡
ካንሲ ይህንን ጥቃት እንደፈጸመ ወዲያውኑ ከዩናይትድ ስቴትስ ወጣ፤ በፓኪስታን ፑብጃብ በተባለ ክፍለ አገር በሰኔ 8 ቀን 1989 ዓ.ም. በቁጥጥር ስር እስኪውልም ድረስ ተፈላጊ ሆኖ ቆየ፡፡ ለፍርድ ለመቅረብም ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ተወሰደ፡፡
በኅዳር 01 ቀን 1990 ዓ.ም. ካንሲ በፌርፋክስ፣ ቨርጂኒያ ጁሪ የሲአይኤ ሠራተኞችን በመግደል ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ ተገኘ፡፡ ካንሲ በኅዳር 05 ቀን 1995 ዓ.ም. የሞት ፍርድ ተፈጽሞበታል፡፡
መረጃ ይስጡ
እርስዎ የበኩልዎን ያድርጉ፡፡ ደህንነቱ የተጠበቀ ዓለም እና ይበልጥ ብሩህ የወደፊት ጊዜን እውን ያድርጉ፡፡ ስለ ወሮታ ለፍትሕ መረጃ ማቀበያ ወይም ቅረቢያ አማራጮች ለማወቅ በዚህ ክሊክ ያድርጉ፡፡
- ታጋቺዎች/ተጠላፊዎች
- ሰሜን ኮሪያ
- ጣልቃገብነት በምርጫ ውስጥ
