Success stories
በፊሊፒንስ የአሜሪካዊያን መታፈን እና መገደል፤
በፊሊፒንስ የአሜሪካዊያን መታፈን እና መገደል፤
ወሮታ ለፍትሕ በፊሊፒንስ፣ ለአቡ ሳያፍ ግሩፕ (ኤኤስጂ) ሽብርተኛ አባል ቶቲንግ ሃኖ በቁጥጥር ስር መዋል ምክንያት የሆነው መረጃ $100,000 ወሮታ ከፍሏል፡፡
ቶቲንግ ክራፍት ሃኖ የኤኤስጂ ቡድን አባል ነበር፤ ይህ ግለሰብ በግንቦት 19 ቀን 1993 ዓ.ም. በፊሊፒንስ፣ በፓላዋን ዶስ ፓልማስ ሪዞርት በሦስት አሜሪካዊያን ዜጎች አፈና ላይ ተሳትፏል፡፡ ሦስቱ አሜሪካዊያንም ጉዊሌርሞ ሶቤሮ እና የዩናይትድ ስቴትስ ሚሲዮን አባላት የትዳር አጋሮቹ ማርቲን እና ጋርሲያ በርንሃም ነበሩ፡፡ በሰኔ 04 ቀን 1993 ዓ.ም. የኤኤስጂ ቃል አቀባይ አቡ ሳያፍ፣ ጉዊሌርሞ ሶቤሮ ለፊሊፒንስ ፕሬዚደንት ግሎሪያ ማካፓጋል-አሮዮ የልደት ስጦታ እንዲሆን መገደሉን ገለጸ፡፡ በመስከረም 27 ቀን 1994 ዓ.ም. በባዚላን ደሴት የሰው አጽም ጭንቅላት ተገኘ፤ ይህ ጭንቅላት የሟች ጉዊሌርሞ ሶቤሮ መሆኑ ተረጋገጠ፡፡ በሰኔ 1994 ዓ.ም. ማርቲን በርንሃም በፊሊፒንስ ወታደሮች እና በኤኤስጂ መካከል በነበረው የተኩስ ልውውጥ ተገደለ፤ ጋርሲያ በርንሃም ብትቆስልም ለመትረፍ እና ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለመመለስ ችላለች፡፡
በታኅሳስ 28 ቀን 1997 ዓ.ም. የፊሊፒንስ የጸጥታ ኃይል በመረጃ ሰጪ ባገኘው መረጃ መሠረት ሃኖን በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡
መረጃ ይስጡ
እርስዎ የበኩልዎን ያድርጉ፡፡ ደህንነቱ የተጠበቀ ዓለም እና ይበልጥ ብሩህ የወደፊት ጊዜን እውን ያድርጉ፡፡ ስለ ወሮታ ለፍትሕ መረጃ ማቀበያ ወይም ቅረቢያ አማራጮች ለማወቅ በዚህ ክሊክ ያድርጉ፡፡
- ታጋቺዎች/ተጠላፊዎች
- ሰሜን ኮሪያ
- ጣልቃገብነት በምርጫ ውስጥ
