ስለ ተቋሙ
ወሮታ ለፍትሕ በ2010 ዓ.ም. በቶጎ ቶጎ፣ ኒጀር ጥቃት በነበረው ተሳትፎ ስለ ኦዉስማን ኢላሶዉ ጂቦ፣ በሌላ ስሙ ፔቲት ቻፖሪ እና ኻሊድ ፎውላኒ መረጃ ለሚሰጥ እስከ $5 ሚሊዮን ወሮታ ይከፍላል፡፡
ጂቦ፣ በግሬተር ሳሃራ (አይሲስ-ጂኤስ)የኢራቅ እና ሶሪያ ኢስላማዊ መንግሥት መሪ ነው፤ የሚንቀሳቀሰውም በመናካ ክልል፣ ማሊ ነው፡፡ ጂቦ የሟች የአይሲስ-ጂኤስ መሪ አደናን አቡ ዋሊድ አል-ሳህራዊ (አቡ ዋሊድ) ቁልፍ የበታች አመራር እና ተባባሪ ነበር፡፡ ጂቦ የአይሲስ-ጂኤስ አባላት በኒጀር እና በአካባቢው አገራት ምዕራባዊያንን ለማገት ወይም ጥቃት ለመፈጸም ኔትወርክ እንዲመሠርቱ መመሪያ ሰጥቷል፡፡ እንዲሁም ጂቦ በበርካታ በአገር ውስጥ የጸጥታ ኃይሎች ላይ በተፈጸሙ በርካታ ጥቃቶች ላይ ተሳትፏል፡፡ በሰኔ 24 ቀን 2011 ዓ.ም. የአይሲስ-ጂኤስ ተዋጊዎች ኢኔትስ፣ ቲላቤሪ ክልል፣ ኒጀር ውስጥ በሚገኙ የናይጄሪያ የጦር ኃይሎች ሰፈር ላይ ጥቃት ፈጽመዋል፡፡ እንዲሁም በግንቦት 06 ቀን 2011 ዓ.ም. በቶጎ ቶጎ አቅራቢያ በናይጄሪያዊያን ወታደሮች ላይ በተፈጸመ የደፈጣ ጥቃት ስድስት የናይጄሪያ ወታደሮች እንዲታገቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
በመስከረም 24 ቀን 2010 ዓ.ም. ቶንጎ ቶንጎ በተባለው የኒጀር መንደር አካባቢ ከአይሲስ – ግሬተር ሰሃራ (አይሲስ-ጂኤስ) ጋር ግንኙነት የነበራቸው ታጣቂዎች ሽብርተኝነትን በመዋጋት ላይ ለነበሩ የናይጄሪያ ሀይሎች ስልጠና፣ ምክር እና እገዛ ለመስጠት ተመድቦ በነበረው የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ ሀይል ላይ የደፈጣ ጥቃት ፈፅመዋል፡፡ በዚህ ጥቃት ምክንያት 4 የዩናይትድ ስቴትስ እና 4 የናይጄሪያ ወታደሮች ሞተዋል፡፡ በዚህ ጥቃት 2 ተጨማሪ አሜሪካውያን እና 8 ናይጄሪያውን ቆስለዋል፡፡ በጥር 04 ቀን 2010 ዓ.ም. የአይሲስ-ጂኤስ መሪ አድናን አቡ ዋሊድ አል-ሳህራዊ ለጥቃቱ ሀላፊነት ወስዷል፡፡
በሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም.፣ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጂቦን ልዩ አለምአቀፍ ሽብርተኛ በማለት በስራ አስፈፃሚ ትእዛዝ (ኤክዘኪውቲቭ ኦርደር) 13224 እንደተሻሻለው መዝግቦታል፡፡ በዚህም መሰረት ሌሎች እርምጃዎች እንደተጠበቁ ሆነው በዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር ወሰን ውስጥ የሚገኙ የጂቦ ንብረቶች እና ጥቅሞች ሁሉ ታግደዋል፣ ማናቸውም የዩናይትድ ስቴትስ ሰዎች ከጂቦ ጋር በምንም አይነት ልውውጥ ላይ መሳተፍ አይፈቀድላቸውም፡፡ በተጨማሪም በዩናይትድ ስቴትስ በውጭ አገር የሚገኝ ሽብርተኛ ድርጅት በሚል ለተመዘገበው አይሲስ-ጂኤስ ሆን ብሎ የማቴሪያል ወይም የሀብቶች አቅርቦት ማድረግ፣ ወይም ለማቅረብ መመሳጠር የተከለከለ ወንጀል ነው፡፡
