ጀማል ሰዒድ አብዱል ራሂም

ምስራቅ አቅራቢያ - ሰሜን አፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ

ወሮታ

እስከ 5 ሚሊዮን ዶላር

የበኩልዎን ያድርጉ

ስለ ተቋሙ

ወሮታ ለፍትሕ ስለ ጀማል ሰዒድ አብዱል ራሂም፣ በሌላ ስሙ አሊ አል ጃሰም ፉዓድ እና ኢስማኤል መረጃ ለሚሰጥ እስከ $5 ሚሊዮን ወሮታ ይከፍላል፡፡ የአቡ ኒዳል ሽብርተኛ ድርጅት አባል ነው የሚባለው ራሂም በነሐሴ 30 ቀን 1978 ዓ.ም. በካራቺ፣ ፓኪስታን በተፈጸመው የፓን አም የበረራ 73 ጠለፋ ለነበረው ሚና ተፈላጊ ነው፡፡ 379 ተሳፋሪዎችን እና የበረራ ሠራተኞችን ለ16 ሰዓታት ያህል አግተው ካቆዩ በኋላ፣ አጋቾቹ በጭፍን ተኩስ ከፈቱ፤ በዚህም ሁለት አሜሪካዊያንን ጨምሮ ሃያ ሰዎች ሲሞቱ፣ ከ100 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቆስለዋል፡፡

በጠለፋው ላይ ለነበረው ተሳትፎ ራሂም በዩናይትድ ስቴትስ ፌደራል ግራንድ ጁሪ ክስ ይመስረትበት የሚል ውሳኔ የተሰጠበት ሲሆን፣ በኤፍቢአይ እጅግ ተፈላጊ ሽብርተኞች ዝርዝር ውስጥ ስሙ ተካቷል፡፡

Skip to content